Khetha Ulimi

mic

Ukwabelana

Yabelana ngesixhumanisi

QR code for https://globalrecordings.net/script/7748

unfoldingWord 01 - ፍጥረት

unfoldingWord 01 - ፍጥረት

Uhlaka: Genesis 1-2

Inombolo Yeskripthi: 1201

Ulimi: Amharic

Itimu: Bible timeline (Creation)

Izilaleli: General

Inhloso: Evangelism; Teaching

Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture

Isimo: Approved

Imibhalo ayiziqondiso eziyisisekelo zokuhunyushwa nokuqoshwa kwezinye izilimi. Kufanele zishintshwe njengoba kunesidingo ukuze ziqondakale futhi zihambisane nesiko nolimi oluhlukene. Amanye amagama nemiqondo esetshenzisiwe ingase idinge incazelo eyengeziwe noma ishintshwe noma ikhishwe ngokuphelele.

Umbhalo Weskripthi

ከዚህ ቀጥሎ የምንመለከተው እግዚአብሔር የሁሉም ነገር ጀማሪ መሆኑን ነው። ስለሆነም እግዚአብሔር ዓለምንና በውስጧ የሚገኙትን ነገሮች በስድስት ቀናት ፈጠረ። እግዚአብሔር ምድርን ከፈጠረ በኋላ ምድር ጨለማና ባዶ ነበረች፤ በውስጧምንም ነገር ገና አልተፈጠረም ነበር። ይሁን እንጂ የእግዚአብሔር መንፈስ በውሆች ላይሰፍፎ ነበር።

ከዚያም እግዚአብሔር “ብርሃን ይሁን” አለ ብርሃንም ሆነ። እግዚአብሔርም ብርሃኑ መልካም እንደሆነ አይቶ “ቀን” ብሎ ጠራው። እግዚአብሔርም ቀኑን ከጨለማ ለይቶ ጨለማውን ሌሊት ብሎ ጠራው። እግዚአብሔርም በመጀመሪያው ቀን ብርሃንን ፈጠረ።

በሁለተኛው ቀን እግዚአብሔር ከምድር በላይ ያለውን ጠፈር ፈጠረ። ስለሆነም እግዚአብሔር ውሃን ከጠፈር ለየ።

በሦስተኛው ቀን እግዚአብሔር ውሃውን ከደረቁ መሬት እንዲለይ አደረገ። እግዚአብሔርም ደረቁን መሬት “ምድር” ውሃውንም “ባሕር” ብሎ ጠራው። እግዚአብሔርም የፈጠረው ነገር መልካም እንደ ሆነ አየ።

ከዚያም እግዚአብሔር ምድር ሁሉንም ዓይነት ዛፎችንና ተክሎችን ታብቅል አለ፣ እንዲሁም ሆነ። እግዚአብሔርም የፈጠረው ነገር መልካም እንደ ሆነ አየ።

በአራተኛው የፍጥረት ቀን እግዚአብሔር ፀሐይን፣ ጨረቃንና ክዋክብትን ፈጠረ። እግዚአብሔር ቀንና ሌሊትንም ወቅቶችንና ዓመታትንም እንዲለዩ አደረገ። እግዚአብሔርም የፈጠረው ነገር መልካም እንደ ሆነ አየ።

በአምስተኛው ቀን እግዚአብሔር በውሃ ውስጥ የሚኖሩትንና ወፎችን ሁሉ ፈጠረ። እግዚአብሔር ያ መልካም እንደ ሆነ አየ የተፈጠሩትንም ባረካቸው።

በስድስተኛውም ቀን፣ እግዚአብሔር “በምድር ላይ ሁሉም ዓይነት እንስሳት ይሁኑ” አለ። እግዚአብሔር እንዳለውም ሆነ። አንዳንዶቹ የእርሻ ከብቶች፣ አንዳንዶቹ በምድር የሚሳቡ፣ አንዳንዶቹ የዱር እንስሳት ነበሩ። እግዚአብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ።

እግዚአብሔር “ሰዎችን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር እነርሱም በምድር ሁሉና በእንስሳት ሁሉ ላይ ሥልጣን ይኑራቸው” አለ።

ስለዚህ እግዚአብሔር ከምድር አፈር ወስዶ ሰው አድርጐ አበጀና የሕይወትን እስትንፋስ ሰጠው። የዚህም ሰው ስም አዳም ተባለ። እግዚአብሔር አዳም በሚኖርበት ስፍራ አትክልት ተከለና እንዲያለማው እዚያው አስቀመጠው።

በአትክልቱም መካከል እግዚአብሔር ሁለት የተለዩ ዛፎችን ተከለ፤ የሕይወት ዛፍና መልካምና ክፉን መለየት የሚያስችል የእውቀት ዛፎች ነበሩ። እግዚአብሔርም አዳምን በአትክልቱ ስፍራ ካለው መልካምንና ክፉን መለየት ከሚያስችለው የእውቀት ዛፍ በቀር በአትክልቱ ውስጥ ካለው ከየትኛውም ዛፍ መብላት እንደሚችል ተናገረው። ነገር ግን ክፉውንና መልካሙን መለየት ከሚያስችለው ዛፍ ቢበላ እንደሚሞት ተናግሮት ነበር።

እግዚአብሔር ሰው ብቻውን መሆኑ መልካም እንዳይደለ ተናገረው። ከእንስሳቱ አንዳቸውም የአዳም ረዳት ሊሆኑ አልቻሉም።

እግዚአብሔርም በአዳም ላይ ከባድ እንቅልፍ ጣለበት አንቀላፍቶም ሳለ ከጐድኑ አንዲት አጥንት ወስዶ ሴት አድርጎ ሠራትና ወደ አዳም አመጣት።

አዳምም ባያት ጊዜ እንዲህ አለ፤ “ይህች እኔኑ ትመስላለች ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል። ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር አንድ ይሆናል።

እግዚአብሔር ወንድና ሴትን በራሱ መልክ ፈጠረ። እግዚአብሔርም ባረካቸው፤ አላቸውም “ብዙ ልጆችና የልጅ ልጆችም ይኑሩአችሁ ምድርንም ሙሉአት” እግዚአብሔርም የሠራው ነገር በጣም ጥሩ እንደ ነበር አየ። በሁሉም ነገር ተደሰተ ይህ ሁሉ በስድስት ቀን ሆነ።

በሰባተኛውም ቀን እግዚአብሔር የመፍጠር ሥራውን ፈጸመ። ስለዚህ እግዚአብሔር ሲሠራው ከነበረው ሥራ ሁሉ አረፈ፤ ሰባተኛውንም ቀን ባረከው ቀደሰውም። ምክንያቱም በዚህ ቀን ከሥራው ሁሉ አርፏልና። እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን በውስጧም የሚገኙትን በፈጠረ ጊዜ የተከናወኑት በዚህ ሁኔታ ነበር።

Ulwazi oluhlobene

Amazwi Okuphila - Imiyalezo yevangeli elalelwayo ngezinkulungwane zezilimi equkethe imiyalezo esekelwe eBhayibhelini mayelana nensindiso nokuphila kobuKristu.

Copyright and Licensing - GRN shares its audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?