언어선택

mic

공유

링크 공유

QR code for https://globalrecordings.net/script/7748

unfoldingWord 01 - ፍጥረት

unfoldingWord 01 - ፍጥረት

개요: Genesis 1-2

스크립트 번호: 1201

언어: Amharic

주제: Bible timeline (Creation)

청중: General

목적: Evangelism; Teaching

Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture

지위: Approved

이 스크립트는 다른 언어로 번역 및 녹음을위한 기본 지침입니다. 그것은 그것이 사용되는 각 영역에 맞게 다른 문화와 언어로 조정되어야 합니다. 사용되는 몇 가지 용어와 개념은 다른 문화에서는 다듬어지거나 생략해야 할 수도 있습니다.

스크립트 텍스트

ከዚህ ቀጥሎ የምንመለከተው እግዚአብሔር የሁሉም ነገር ጀማሪ መሆኑን ነው። ስለሆነም እግዚአብሔር ዓለምንና በውስጧ የሚገኙትን ነገሮች በስድስት ቀናት ፈጠረ። እግዚአብሔር ምድርን ከፈጠረ በኋላ ምድር ጨለማና ባዶ ነበረች፤ በውስጧምንም ነገር ገና አልተፈጠረም ነበር። ይሁን እንጂ የእግዚአብሔር መንፈስ በውሆች ላይሰፍፎ ነበር።

ከዚያም እግዚአብሔር “ብርሃን ይሁን” አለ ብርሃንም ሆነ። እግዚአብሔርም ብርሃኑ መልካም እንደሆነ አይቶ “ቀን” ብሎ ጠራው። እግዚአብሔርም ቀኑን ከጨለማ ለይቶ ጨለማውን ሌሊት ብሎ ጠራው። እግዚአብሔርም በመጀመሪያው ቀን ብርሃንን ፈጠረ።

በሁለተኛው ቀን እግዚአብሔር ከምድር በላይ ያለውን ጠፈር ፈጠረ። ስለሆነም እግዚአብሔር ውሃን ከጠፈር ለየ።

በሦስተኛው ቀን እግዚአብሔር ውሃውን ከደረቁ መሬት እንዲለይ አደረገ። እግዚአብሔርም ደረቁን መሬት “ምድር” ውሃውንም “ባሕር” ብሎ ጠራው። እግዚአብሔርም የፈጠረው ነገር መልካም እንደ ሆነ አየ።

ከዚያም እግዚአብሔር ምድር ሁሉንም ዓይነት ዛፎችንና ተክሎችን ታብቅል አለ፣ እንዲሁም ሆነ። እግዚአብሔርም የፈጠረው ነገር መልካም እንደ ሆነ አየ።

በአራተኛው የፍጥረት ቀን እግዚአብሔር ፀሐይን፣ ጨረቃንና ክዋክብትን ፈጠረ። እግዚአብሔር ቀንና ሌሊትንም ወቅቶችንና ዓመታትንም እንዲለዩ አደረገ። እግዚአብሔርም የፈጠረው ነገር መልካም እንደ ሆነ አየ።

በአምስተኛው ቀን እግዚአብሔር በውሃ ውስጥ የሚኖሩትንና ወፎችን ሁሉ ፈጠረ። እግዚአብሔር ያ መልካም እንደ ሆነ አየ የተፈጠሩትንም ባረካቸው።

በስድስተኛውም ቀን፣ እግዚአብሔር “በምድር ላይ ሁሉም ዓይነት እንስሳት ይሁኑ” አለ። እግዚአብሔር እንዳለውም ሆነ። አንዳንዶቹ የእርሻ ከብቶች፣ አንዳንዶቹ በምድር የሚሳቡ፣ አንዳንዶቹ የዱር እንስሳት ነበሩ። እግዚአብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ።

እግዚአብሔር “ሰዎችን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር እነርሱም በምድር ሁሉና በእንስሳት ሁሉ ላይ ሥልጣን ይኑራቸው” አለ።

ስለዚህ እግዚአብሔር ከምድር አፈር ወስዶ ሰው አድርጐ አበጀና የሕይወትን እስትንፋስ ሰጠው። የዚህም ሰው ስም አዳም ተባለ። እግዚአብሔር አዳም በሚኖርበት ስፍራ አትክልት ተከለና እንዲያለማው እዚያው አስቀመጠው።

በአትክልቱም መካከል እግዚአብሔር ሁለት የተለዩ ዛፎችን ተከለ፤ የሕይወት ዛፍና መልካምና ክፉን መለየት የሚያስችል የእውቀት ዛፎች ነበሩ። እግዚአብሔርም አዳምን በአትክልቱ ስፍራ ካለው መልካምንና ክፉን መለየት ከሚያስችለው የእውቀት ዛፍ በቀር በአትክልቱ ውስጥ ካለው ከየትኛውም ዛፍ መብላት እንደሚችል ተናገረው። ነገር ግን ክፉውንና መልካሙን መለየት ከሚያስችለው ዛፍ ቢበላ እንደሚሞት ተናግሮት ነበር።

እግዚአብሔር ሰው ብቻውን መሆኑ መልካም እንዳይደለ ተናገረው። ከእንስሳቱ አንዳቸውም የአዳም ረዳት ሊሆኑ አልቻሉም።

እግዚአብሔርም በአዳም ላይ ከባድ እንቅልፍ ጣለበት አንቀላፍቶም ሳለ ከጐድኑ አንዲት አጥንት ወስዶ ሴት አድርጎ ሠራትና ወደ አዳም አመጣት።

አዳምም ባያት ጊዜ እንዲህ አለ፤ “ይህች እኔኑ ትመስላለች ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል። ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር አንድ ይሆናል።

እግዚአብሔር ወንድና ሴትን በራሱ መልክ ፈጠረ። እግዚአብሔርም ባረካቸው፤ አላቸውም “ብዙ ልጆችና የልጅ ልጆችም ይኑሩአችሁ ምድርንም ሙሉአት” እግዚአብሔርም የሠራው ነገር በጣም ጥሩ እንደ ነበር አየ። በሁሉም ነገር ተደሰተ ይህ ሁሉ በስድስት ቀን ሆነ።

በሰባተኛውም ቀን እግዚአብሔር የመፍጠር ሥራውን ፈጸመ። ስለዚህ እግዚአብሔር ሲሠራው ከነበረው ሥራ ሁሉ አረፈ፤ ሰባተኛውንም ቀን ባረከው ቀደሰውም። ምክንያቱም በዚህ ቀን ከሥራው ሁሉ አርፏልና። እግዚአብሔር ሰማይንና ምድርን በውስጧም የሚገኙትን በፈጠረ ጊዜ የተከናወኑት በዚህ ሁኔታ ነበር።

관련정보

생명의 말씀 - GRN 은 성경에 기반한 구원과 그리스도인의 삶에 대한 수천개의 오디오 복음 메시지를 가지고 있습니다.

Copyright and Licensing - GRN shares its audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?