unfoldingWord 31 - ኢየሱስ በውሃ ላይ ተራመደ
Muhtasari: Matthew 14:22-33; Mark 6:45-52; John 6:16-21
Nambari ya Hati: 1231
Lugha: Amharic
Hadhira: General
Kusudi: Evangelism; Teaching
Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture
Hali: Approved
Hati ni miongozo ya kimsingi ya kutafsiri na kurekodi katika lugha zingine. Yanafaa kurekebishwa inavyohitajika ili kuzifanya zieleweke na kufaa kwa kila utamaduni na lugha tofauti. Baadhi ya maneno na dhana zinazotumiwa zinaweza kuhitaji maelezo zaidi au hata kubadilishwa au kuachwa kabisa.
Maandishi ya Hati
ከዚያም ኢየሱስ ሕዝቡን እያሰናበተ እያለ ጀልባ ውስጥ ገብተው እየቀዘፉ ወደ ማዶ እንዲሻገሩ ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው። ኢየሱስ ሕዝቡን ካሰናበተ በኋላ ለመጸለይ ወደ ተራራ ወጣ። በዚያ ኢየሱስ ብቻውን ነበር፣ እስከ እኩለ ሌሊትም ጸለየ።
በዚሁ ጊዜ፣ ደቀ መዛሙርቱ ጀልባቸውን እየቀዘፉ ነበር፣ በእኩለ ሌሊት የደረሱት ወደ ሐይቁ አጋማሽ ብቻ ነበር። ነፋሱ በእነርሱ ላይ በኃይል ይነፍስ ስለ ነበር የሚቀዝፉት በጣም በችግር ነበር።
በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መጸለዩን ጨረሰና ወደ ደቀ መዛሙርቱ ሄደ። በውሃው ላይ እየተራመደ ሐይቁን አቋርጦ ወደ ጀልባቸው ሄደ!
ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስን ባዩ ጊዜ በጣም ፈሩ፣ ምክንያቱም ምትሐት ያዩ መሰላቸው፣ ኢየሱስ የፈሩ መሆናቸውን ዐወቀ፣ ስለዚህ ወደ እነርሱ ተጣራና፣ “አትፍሩ። እኔ ነኝ!” አላቸው።
በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ ኢየሱስን፣ “መምህር ሆይ፣ አንተስ ከሆንክ በውሃው ላይ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዝ” አለው። ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ “ና!” አለው።
ስለዚህ ጴጥሮስ ከጀልባው ወጣና በውሃው ላይ ወደ ኢየሱስ መራመድ ጀመረ። ነገር ግን አጭር ርቀት ከተራመደ በኋላ ዓይኖቹን ከኢየሱስ አዞረና ማዕበሉን ያይ ብርቱው ነፋስም ይሰማው ጀመር።
በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ ፈራና በውሃው መስጠም ጀመረ። “መምህር ሆይ፣ አድነኝ!” ብሎ ጮኸ። ኢየሱስ ወዲያው እጆቹን ዘረጋና ያዘው። ከዚያም ጴጥሮስን፣ “አንተ እምነት የጎደለህ፣ ለምን ተጠራጠርህ?” አለው።
ጴጥሮስና ኢየሱስ ወደ ጀልባው በገቡ ጊዜ፣ ነፋሱ መንፈሱን ወዲያውኑ አቆመና ጸጥ አለ። ደቀ መዛሙርቱ ተደነቁ። “በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ” በማለት ለኢየሱስ ሰገዱለት።