Ընտրեք լեզու

mic

Կիսվել

Կիսվել հղումով

QR code for https://globalrecordings.net/script/7778

unfoldingWord 31 - ኢየሱስ በውሃ ላይ ተራመደ

unfoldingWord 31 - ኢየሱስ በውሃ ላይ ተራመደ

Ուրվագիծ: Matthew 14:22-33; Mark 6:45-52; John 6:16-21

Սցենարի համարը: 1231

Լեզու: Amharic

Հանդիսատես: General

Նպատակը: Evangelism; Teaching

Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture

Կարգավիճակ: Approved

Սցենարները հիմնական ուղեցույցներ են այլ լեզուներով թարգմանության և ձայնագրման համար: Դրանք պետք է հարմարեցվեն ըստ անհրաժեշտության, որպեսզի դրանք հասկանալի և համապատասխան լինեն յուրաքանչյուր տարբեր մշակույթի և լեզվի համար: Օգտագործված որոշ տերմիններ և հասկացություններ կարող են ավելի շատ բացատրության կարիք ունենալ կամ նույնիսկ փոխարինվել կամ ամբողջությամբ բաց թողնել:

Սցենարի տեքստ

ከዚያም ኢየሱስ ሕዝቡን እያሰናበተ እያለ ጀልባ ውስጥ ገብተው እየቀዘፉ ወደ ማዶ እንዲሻገሩ ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው። ኢየሱስ ሕዝቡን ካሰናበተ በኋላ ለመጸለይ ወደ ተራራ ወጣ። በዚያ ኢየሱስ ብቻውን ነበር፣ እስከ እኩለ ሌሊትም ጸለየ።

በዚሁ ጊዜ፣ ደቀ መዛሙርቱ ጀልባቸውን እየቀዘፉ ነበር፣ በእኩለ ሌሊት የደረሱት ወደ ሐይቁ አጋማሽ ብቻ ነበር። ነፋሱ በእነርሱ ላይ በኃይል ይነፍስ ስለ ነበር የሚቀዝፉት በጣም በችግር ነበር።

በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መጸለዩን ጨረሰና ወደ ደቀ መዛሙርቱ ሄደ። በውሃው ላይ እየተራመደ ሐይቁን አቋርጦ ወደ ጀልባቸው ሄደ!

ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስን ባዩ ጊዜ በጣም ፈሩ፣ ምክንያቱም ምትሐት ያዩ መሰላቸው፣ ኢየሱስ የፈሩ መሆናቸውን ዐወቀ፣ ስለዚህ ወደ እነርሱ ተጣራና፣ “አትፍሩ። እኔ ነኝ!” አላቸው።

በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ ኢየሱስን፣ “መምህር ሆይ፣ አንተስ ከሆንክ በውሃው ላይ ወደ አንተ እንድመጣ እዘዝ” አለው። ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ “ና!” አለው።

ስለዚህ ጴጥሮስ ከጀልባው ወጣና በውሃው ላይ ወደ ኢየሱስ መራመድ ጀመረ። ነገር ግን አጭር ርቀት ከተራመደ በኋላ ዓይኖቹን ከኢየሱስ አዞረና ማዕበሉን ያይ ብርቱው ነፋስም ይሰማው ጀመር።

በዚያን ጊዜ ጴጥሮስ ፈራና በውሃው መስጠም ጀመረ። “መምህር ሆይ፣ አድነኝ!” ብሎ ጮኸ። ኢየሱስ ወዲያው እጆቹን ዘረጋና ያዘው። ከዚያም ጴጥሮስን፣ “አንተ እምነት የጎደለህ፣ ለምን ተጠራጠርህ?” አለው።

ጴጥሮስና ኢየሱስ ወደ ጀልባው በገቡ ጊዜ፣ ነፋሱ መንፈሱን ወዲያውኑ አቆመና ጸጥ አለ። ደቀ መዛሙርቱ ተደነቁ። “በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ” በማለት ለኢየሱስ ሰገዱለት።

Առնչվող տեղեկություններ

Կյանքի խոսքեր - Աուդիո ավետարանական ուղերձներ հազարավոր լեզուներով, որոնք պարունակում են Աստվածաշնչի վրա հիմնված ուղերձներ փրկության և քրիստոնեական կյանքի մասին:

Copyright and Licensing - GRN shares its audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?