unfoldingWord 24 - ዮሐንስ ኢየሱስን አጠመቀ
Kontūras: Matthew 3; Mark 1; Luke 3; John 1:15-37
Scenarijaus numeris: 1224
Kalba: Amharic
Publika: General
Tikslas: Evangelism; Teaching
Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture
Būsena: Approved
Scenarijai yra pagrindinės vertimo ir įrašymo į kitas kalbas gairės. Prireikus jie turėtų būti pritaikyti, kad būtų suprantami ir tinkami kiekvienai kultūrai ir kalbai. Kai kuriuos vartojamus terminus ir sąvokas gali prireikti daugiau paaiškinti arba jie gali būti pakeisti arba visiškai praleisti.
Scenarijaus tekstas
የዘካርያስና የኤልሳቤጥ ልጅ ዮሐንስ አደገና ነቢይ ሆነ። በምድረ በዳ ኖረ፣ የበረሐ ማርና አንበጣ ተመገበ፣ ከግመል ፀጉር የተሠራ ልብስም ለበሰ።
ብዙ ሕዝብ ዮሐንስን ለመስማት ወደ ምድረ በዳ መጡ። እርሱም፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ” በማለት ሰበከላቸው።
ሕዝቡ የዮሐንስን መልእክት በሰሙ ጊዜ፣ አብዛኞቻቸው ኃጢአታቸውን ተናዘዙ፣ ዮሐንስም አጠመቃቸው። ብዙ የሃይማኖት መሪዎች ደግሞ በዮሐንስ ሊጠመቁ መጡ፣ ነገር ግን ንስሐ አልገቡም ወይም ኃጢአታቸውን አልተናዘዙም።
ዮሐንስ ለሃይማኖት መሪዎቹ እንዲህ አላቸው፣ “እናንተ መርዛማ እባቦች! ንስሐ ግቡና ድርጊታችሁን ለውጡ። መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ሁሉ ይቈረጥና ወደ እሳት ይጣላል።” ዮሐንስ ነቢያት “እነሆ፣ መንገድህን የሚያዘጋጅ መልእክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ።” በማለት የተናገሩትን ፈጽመ።
አንዳንድ አይሁዶች መሲሕ ስለ መሆኑ ዮሐንስን ጠየቁት። ዮሐንስ እንዲህ ብሎ መለሰ፣ “እኔ መሲሑ አይደለሁም፣ ነገር ግን ከእኔ በኋላ የሚመጣ አንድ ሰው አለ። የጫማውን ማሰሪያ ልፈታ እንኳ የማይገባኝ በጣም ታላቅ ነው።”
በቀጣዩ ቀን፣ ኢየሱስ በዮሐንስ ለመጠመቅ መጣ። ዮሐንስ ባየው ጊዜ፣ “ተመልከቱ! እነሆ፣ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ” አለ።
ዮሐንስ ኢየሱስን፣ “እኔ አንተን ለማጥመቅ ተገቢ ሰው አይደለሁም። በዚህ ፈንታ አንተ እኔን ማጥመቅ አለብህ እንጂ” አለው። ኢየሱስ ግን፣ “መደረግ ያለበት ትክክለኛ ነገር ነውና አንተ እኔን ማጥመቅ ይገባሃል” አለ። ስለዚህ ኢየሱስ ከቶ ኃጢአት ባይሠራም እንኳ ዮሐንስ ኢየሱስን አጠመቀው።
ኢየሱስ ከተጠመቀ በኋላ ከውኃው እንደ ወጣ፣ የእግዚአብሔር መንፈስ በርግብ አምሳል ታየና ወርዶ በእርሱ ላይ ዐረፈ። በዚሁ ጊዜ የእግዚአብሔር ድምፅ ከሰማይ፣ “አንተ እኔ የምወድህ ልጄ ነህ፣ በአንተም በጣም ደስ ብሎኛል” ብሎ ተናገረ።
እግዚአብሔር ለዮሐንስ፣ “መንፈስ ቅዱስ ይወርድና አንተ በምታጠምቀው ሰው ላይ ያርፋል። ሰውዬው የእግዚአብሔር ልጅ ነው” ብሎ ተናግሮት ነበር። አንድ አምላክ ብቻ አለ። ነገር ግን ዮሐንስ ኢየሱስን ባጠመቀው ጊዜ፣ እግዚአብሔር አብ ሲናገር ሰማ፣ እግዚአብሔር ወልድን ዐየ፣ እርሱም ኢየሱስ ነው፣ እንዲሁም መንፈስ ቅዱስን ዐየ።