Veldu tungumál

mic

unfoldingWord 24 - ዮሐንስ ኢየሱስን አጠመቀ

unfoldingWord 24 - ዮሐንስ ኢየሱስን አጠመቀ

Útlínur: Matthew 3; Mark 1; Luke 3; John 1:15-37

Handritsnúmer: 1224

Tungumál: Amharic

Áhorfendur: General

Tilgangur: Evangelism; Teaching

Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture

Staða: Approved

Forskriftir eru grunnleiðbeiningar fyrir þýðingar og upptökur á önnur tungumál. Þau ættu að vera aðlöguð eftir þörfum til að gera þau skiljanleg og viðeigandi fyrir hverja menningu og tungumál. Sum hugtök og hugtök sem notuð eru gætu þurft frekari skýringar eða jafnvel skipt út eða sleppt alveg.

Handritstexti

የዘካርያስና የኤልሳቤጥ ልጅ ዮሐንስ አደገና ነቢይ ሆነ። በምድረ በዳ ኖረ፣ የበረሐ ማርና አንበጣ ተመገበ፣ ከግመል ፀጉር የተሠራ ልብስም ለበሰ።

ብዙ ሕዝብ ዮሐንስን ለመስማት ወደ ምድረ በዳ መጡ። እርሱም፣ “የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ” በማለት ሰበከላቸው።

ሕዝቡ የዮሐንስን መልእክት በሰሙ ጊዜ፣ አብዛኞቻቸው ኃጢአታቸውን ተናዘዙ፣ ዮሐንስም አጠመቃቸው። ብዙ የሃይማኖት መሪዎች ደግሞ በዮሐንስ ሊጠመቁ መጡ፣ ነገር ግን ንስሐ አልገቡም ወይም ኃጢአታቸውን አልተናዘዙም።

ዮሐንስ ለሃይማኖት መሪዎቹ እንዲህ አላቸው፣ “እናንተ መርዛማ እባቦች! ንስሐ ግቡና ድርጊታችሁን ለውጡ። መልካም ፍሬ የማያፈራ ዛፍ ሁሉ ይቈረጥና ወደ እሳት ይጣላል።” ዮሐንስ ነቢያት “እነሆ፣ መንገድህን የሚያዘጋጅ መልእክተኛዬን በፊትህ እልካለሁ።” በማለት የተናገሩትን ፈጽመ።

አንዳንድ አይሁዶች መሲሕ ስለ መሆኑ ዮሐንስን ጠየቁት። ዮሐንስ እንዲህ ብሎ መለሰ፣ “እኔ መሲሑ አይደለሁም፣ ነገር ግን ከእኔ በኋላ የሚመጣ አንድ ሰው አለ። የጫማውን ማሰሪያ ልፈታ እንኳ የማይገባኝ በጣም ታላቅ ነው።”

በቀጣዩ ቀን፣ ኢየሱስ በዮሐንስ ለመጠመቅ መጣ። ዮሐንስ ባየው ጊዜ፣ “ተመልከቱ! እነሆ፣ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ” አለ።

ዮሐንስ ኢየሱስን፣ “እኔ አንተን ለማጥመቅ ተገቢ ሰው አይደለሁም። በዚህ ፈንታ አንተ እኔን ማጥመቅ አለብህ እንጂ” አለው። ኢየሱስ ግን፣ “መደረግ ያለበት ትክክለኛ ነገር ነውና አንተ እኔን ማጥመቅ ይገባሃል” አለ። ስለዚህ ኢየሱስ ከቶ ኃጢአት ባይሠራም እንኳ ዮሐንስ ኢየሱስን አጠመቀው።

ኢየሱስ ከተጠመቀ በኋላ ከውኃው እንደ ወጣ፣ የእግዚአብሔር መንፈስ በርግብ አምሳል ታየና ወርዶ በእርሱ ላይ ዐረፈ። በዚሁ ጊዜ የእግዚአብሔር ድምፅ ከሰማይ፣ “አንተ እኔ የምወድህ ልጄ ነህ፣ በአንተም በጣም ደስ ብሎኛል” ብሎ ተናገረ።

እግዚአብሔር ለዮሐንስ፣ “መንፈስ ቅዱስ ይወርድና አንተ በምታጠምቀው ሰው ላይ ያርፋል። ሰውዬው የእግዚአብሔር ልጅ ነው” ብሎ ተናግሮት ነበር። አንድ አምላክ ብቻ አለ። ነገር ግን ዮሐንስ ኢየሱስን ባጠመቀው ጊዜ፣ እግዚአብሔር አብ ሲናገር ሰማ፣ እግዚአብሔር ወልድን ዐየ፣ እርሱም ኢየሱስ ነው፣ እንዲሁም መንፈስ ቅዱስን ዐየ።

Tengdar upplýsingar

Orð lífsins - Hljóðboðskapur í guðspjalli á þúsundum tungumála sem inniheldur biblíutengdan boðskap um hjálpræði og kristna lífsstíl.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares its audio, video and written scripts under Creative Commons