Seleccioneu un idioma

mic

unfoldingWord 30 - ኢየሱስ አምስት ሺህ ሰዎችን መገበ

unfoldingWord 30 - ኢየሱስ አምስት ሺህ ሰዎችን መገበ

Esquema: Matthew 14:13-21; Mark 6:31-44; Luke 9:10-17; John 6:5-15

Número de guió: 1230

Llenguatge: Amharic

Públic: General

Propòsit: Evangelism; Teaching

Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture

Estat: Approved

Els scripts són pautes bàsiques per a la traducció i l'enregistrament a altres idiomes. S'han d'adaptar segons sigui necessari perquè siguin comprensibles i rellevants per a cada cultura i llengua diferents. Alguns termes i conceptes utilitzats poden necessitar més explicació o fins i tot substituir-se o ometre completament.

Text del guió

ኢየሱስ በተለያዩ ብዙ መንደሮች እንዲሰብኩና ሰዎችን እንዲያስተምሩ ሐዋርያቱን ላከ። እነርሱ ኢየሱስ ወደ ነበረበት በተመለሱጊዜ፣ ያደረጉትንነገር ነገሩት።ከዚያ በኋላ ኢየሱስ ሐይቁን ተሻግረውጸጥታ ወዳለበት ቦታ አብረውት እንዲሄዱናጥቂት እንዲያርፉ ጋበዛቸው። ስለዚህጀልባ ውስጥ ገቡና ሐይቁን ተሻገሩ።

ነገር ግን በጀልባውሲሄዱ ኢየሱስንና ደቀ መዛሙርቱን ያዩአቸው ብዙሰዎች ነበሩ። እነዚህሰዎች ሊቀድሙአቸው በባሕሩዳርቻ ሮጡ። ስለዚህ ኢየሱስና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ማዶ በደረሱጊዜ፣ በጣም ብዙሰዎች አስቀድመውበዚያ ተገኝተው ይጠባበቁአቸው ነበር።

ሕዝቡ ሴቶችና ልጆች ሳይቈጠሩ ከ5000 በላይ ወንዶች ነበሩ። ኢየሱስ ለሕዝቡ እጅግ አዘነላቸው። ለኢየሱስ እነዚህ ሕዝብ እረኛ እንደሌላቸው በጎች ነበሩ። ስለዚህ አስተማራቸውና በመካከላቸው የነበሩትን በሽተኞች ፈወሳቸው።

በዚያ ምሽት ደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ብለው ነገሩት፣ “ጊዜው መሽቶአልና በአቅራቢያው ከተሞች የሉም። የሚበሉትን ነገር ይገዙ ዘንድ ሕዝቡን አሰናብታቸው።”

ኢየሱስ ግን ደቀ መዛሙርቱን፣ “የሚበሉትን እናንተ ስጡአቸው!” አላቸው። እነርሱም፣“ይህን ማድረግ እንዴት እንችላለን? ያለን አምስት እንጀራናሁለት ዓሣ ብቻ ነው”ብለው መለሱለት።

ሃምሳ ሃምሳ ሆነው ሣሩ ላይ እንዲቀመጡ ለሕዝቡ ይነግሩ ዘንድ ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው።

ከዚያም ኢየሱስ አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሣ ይዞ ወደ ሰማይ ተመለከተ፣ ስለ ምግቡም እግዚአብሔርን አመሰገነ።

ከዚያም ኢየሱስ እንጀራውንና ዓሣውን ቈረሰ። ለሕዝቡ እንዲያቀርቡም ለደቀ መዛሙርቱ ሰጣቸው። ደቀ መዛሙርቱ ምግቡን ማደላቸውን ቀጠሉ፣ ከቶም አላለቀም! ሕዝቡ ሁሉ በልተው ጠገቡ።

ከዚያ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ቊርስራሹን ምግብ ሰበሰቡ፣ እርሱም ዐሥራ ሁለት መሶብ ሙሉ ነበር! ምግቡ ሁሉ የመጣው ከአምስቱ እንጀራና ከሁለቱ ዓሣ ነበር።

Informació relacionada

Paraules de vida - Missatges evangèlics d'àudio en milers d'idiomes que contenen missatges basats en la Bíblia sobre la salvació i la vida cristiana.

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?

Copyright and Licensing - GRN shares its audio, video and written scripts under Creative Commons