Изберете език

mic

Дял

Сподели връзка

QR code for https://globalrecordings.net/script/7751

unfoldingWord 04 - የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ከአብርሃም ጋር

unfoldingWord 04 - የእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ከአብርሃም ጋር

Контур: Genesis 11-15

Номер на скрипта: 1204

език: Amharic

Тема: Living as a Christian (Obedience, Leaving old way, begin new way); Sin and Satan (Judgement, Heart, soul of man)

Публика: General

Предназначение: Evangelism; Teaching

Features: Bible Stories; Paraphrase Scripture

Статус: Approved

Сценариите са основни насоки за превод и запис на други езици. Те трябва да бъдат адаптирани, ако е необходимо, за да станат разбираеми и подходящи за всяка различна култура и език. Някои използвани термини и понятия може да се нуждаят от повече обяснения или дори да бъдат заменени или пропуснати напълно.

Текст на сценария

ከጥፋት ውሃው ከብዙ ዓመታትበኋላ ሕዝቦች በዓለም ላይ እንደገና በዙ።ሁሉም አንድ አይነትቋንቋ ይናገሩ ነበር። እግዚአብሔር እንዳዘዛቸው ምድርን ከመሙላትይልቅ በአንድነት ተሰብስበውከተማ ሠሩ።

እነርሱም በጣም ትምክህተኞችና እግዚአብሔር ለተናገራቸው ነገር ያልተጠነቀቁ ነበሩ። እንዲያውም ወደ ሰማይ ሊደርሱ ረጅም ሕንጻ መገንባት ጀመሩ። እግዚአብሔርም እነዚህ ሰዎች ክፉ መሥራታቸውንና በዚህም መቀጠላቸውን አየ። ከዚህም የከፋ ኃጢአት ማድረግ ይችሉም ነበር።

ስለዚህም እግዚአብሔር ቋንቋቸውን ወደ ብዙ የተለያዩ ቋንቋዎች ለወጠና ሕዝቡን በዓለም ሁሉ በተናቸው። ሊሠሩት የጀመሩት ከተማ ስም ባቢሎን ይባላል። የስሙም ትርጓሜ የተደባለቀ ወይም ግራ የተጋባ ማለት ነው።

ከመቶ ዓመታት በኋላ እግዚአብሔር አብራም የተባለውን ሰው ተናገረው። እግዚአብሔርም እንዲህ አለው አገርህንና ቤተ ሰብህን ትተህ እኔ ወደማሳይህ ምድር ሂድ። በዚያም እባርክሃለሁ፣ ታላቅ ሕዝብም አደርግሃለሁ ስምህንም ታላቅ አደርገዋለሁ፣ የሚባርኩህን እባርካለሁ፣ የሚረግሙህንም እረግማለሁ ባንተ ምክንያትም የምድር ሰዎች ሁሉ ይባረካሉ።

አብራምም እግዚአብሔርን ታዘዘ ሚስቱን ሦራንና አገልጋዮቹን ሁሉና ንብረቱንም ሁሉ ይዞ እግዚአብሔር ወዳሳየው የከነዓን ምድር ሄደ።

አብራም ከነዓን በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር “በዙሪያህ ያለውን ሁሉ ተመልከት የምታየውን ምድር ሁሉ ለአንተና ለዘሮችህ ውርስ አድርጌ እሰጣችኋለሁ” አለው። አብራምም በምድር ተቀመጠ።

ከዕለታት አንድ ቀን አብራም መልከ ጼዴቅ የተባለውን ታላቁን የእግዚአብሔር ሊቀ ካህናት ተገናኘው። መልከ ጻዴቅም አብራምን ባረከው እንዲህም አለው “የሰማይና የምድር ጌታ ታላቁ እግዚአብሔር አብራምን ይባርክ” አብራምም ለመልከ ጼዴቅ ካለው ሁሉ አሥራት ሰጠው።

ብዙ ዓመታት ቢያልፉም አብራምና ሦራ አሁንም ያለ ልጅ ይኖሩ ነበር። እግዚአብሔር ለአብራም እንደ ገና ተስፋ ሰጠው ልጅ እንደሚኖረውና ዘሮቹ እንደ ሰማይ ክዋክብት እንደሚበዙ ተናገረው። አብራምም በእግዚአብሔር ተስፋ አመነ። አብራምም በእግዚአብሔር ተስፋ በማመኑ ምክንያት ጻድቅ ሆኖ ተቈጠረ።

እግዚአብሔርምከአብራም ጋር ቃልኪዳን አደረገ። ቃልኪዳን በሁለት ወገኖች መካከል የሚደረግ ስምምነት ነው። እግዚአብሔርም አብራምን“ከገዛ አብራክህ ልጅእሰጥሃለሁ” አለው።“ለዘሮችህም የከነዓንን ምድር እሰጣለሁ።” አብራምግን በዚያን ጊዜ ያለ ልጅ ነበር።

Свързана информация

Думи на живота - Аудио евангелски послания на хиляди езици, съдържащи библейски послания за спасение и християнски живот.

Copyright and Licensing - GRN shares its audio, video and written scripts under Creative Commons

Choosing the audio or video format to download - What audio and video file formats are available from GRN, and which one is best to use?